በሰሜን ሸዋ ሀገረ ስብከት የተባባሰው አለመግባባት


  • ቋሚ ሲኖዶስ በሰሜን ሸዋ ሀገረ ስብከት የተባባሰውን አለመግባባት የሚያጠና ልኡክ ሠየመ
  • “አለመግባባቱን በውይይት እና በምክክር ለመፍታት ከማይቻልበት ደረጃ ላይ ደርሷል” (የዞኑ ፍትሕ ጽ/ቤት)
(ደጀ ሰላም፤ ሜይ 10/2011) በሰሜን ሸዋ ሀገረ ስብከት በቤተ ዘመዳዊ አሠራር ላይ ተመሥርቶ የሚፈጸመውን ሙስና፣ አስተዳደራዊ በደል እና ሥነ ምግባራዊ ጉድለት በመቃወም ችግሩ እልባት እንዲሰጠው የሚደረገው እንቅስቃሴ ተጠናክሯል፡፡ ቀደም ሲል በተቃውሞ እንቅስቃሴው የሀገረ ስብከቱ ጽ/ቤት እና የወረዳ ቤተ ክህነት ሠራተኞች በአንድነት፣ “ጥሩ ሥነ ምግባር እና የጸዳ ሃይማኖት የለውም፤ በመንፈሳዊ አገልግሎታችን ላይ ከፍተኛ ተጽዕኖ አድርሶብናል፤ በተጭበረበረ የሁለተኛ ደረጃ መልቀቂያ ፈተና ውጤት ወደ ቅድስት ሥላሴ መንፈሳዊ ኮሌጅ ገብቶ ዲፕሎማ በመያዝ ቤተ ክርስቲያንን ደፍሯል፤ መንግሥትን አታልሏል” ባሉት የሀገረ ስብከቱ የሰንበት ት/ቤት ክፍል ሓላፊ ላይ ርምጃ እንዲወስድ (የቴዎሎጂ ዲፕሎማው እንዲሰረዝ እና የሚመለከታቸው ሁሉ እንዲያውቁት) ለሀገረ ስብከቱ ጽ/ቤት ቢያመለክቱም ጽ/ቤቱ ወገንተኛ አቋም በመያዝ ሕገ ወጡን ተግባር ለማስተባበል ከደብረ ብርሃን እስከ ጠቅላይ ቤተ ክህነቱ ድረስ መማጠንን መርጧል ተብሏል፡፡

(Read More ወደሚቀጥለው ገጽ ይዞራል . . . . .)