ልደትን በግቢያቸው እንዳያከብሩ በመታገዳቸው የተቃወሙ ተማሪዎች በፖሊስ ታግተዋል


  • ትናንት ሌሊቱን ከአ.አ.ዩ አራት ኪሎ ካምፓስ ከተወሰዱ ተማሪዎች 21ዱ አልተመለሱም፤
  •  በባሕር ዳር፣ ደብረ ብርሃን እና ወላይታ ሶዶ ዩኒቨርሲቲዎች ተመሳሳይ እግድ ተላልፏል፤
  •  ከተማሪው ተወካዮች ጋራ የተወያዩት የጠቅላይ ቤተ ክህነት ሐላፊዎች የዩኒቨርሲቲውን  አስተዳደር አነጋግረዋል፤
  • ‹‹እግዱ በሃይማኖታዊ ማንነታችን እየደረሰብን ላለው መድልዎ አስከፊ መገለጫ ነው፡፡››  (ተማሪዎች)                
  • ‹‹ዩኒቨርሲቲው የአካዳሚ ተቋም እንጂ ቤተ ክርስቲያን አይደለም፡፡›› (አስተዳደሩ)
 (ደጀ ሰላም፤ ጃኑዋሪ 6/2010 ታኅሣሥ 28/2003 .)ከጌታችን ዘጠኙ ዐበይት በዓላት መካከል ልደተ እግዚእ እና ትንሣኤ የኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ሃይማኖት ተከታይ በሆኑ የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ተማሪዎች ዘንድ በድምቀት ሲከበሩ ቆይተዋል፡፡ ከበዓላቱ አስቀድሞ ያሉትን መዋዕለ አጽዋማት ሲከታተሉ የሚቆዩት ተማሪዎቹ በዋዜማው እኩለ ሌሊት ላይ ከሚከናወነው ሥርዓተ ቅዳሴ አስቀድሞ በአጥቢያ አብያተ ክርስቲያን እና በከፍተኛ ትምህርት ተቋማቱ በሚገኙ አዳራሾች በዓላቱን የተመለከቱ የሥነ ጽሑፍ፣ ቃለ ስብከት እና መዝሙራት ዝግቶጅችን በማቅረብ ማክበር ከጀመሩ ዓመታት ተቆጥረዋል፡፡

(Read More ወደሚቀጥለው ገጽ ይዞራል . . . . .)