የቀዳማዊ ኃይለ ሥላሴ ባለሥልጣናት ቤተሰቦች "ለደርግ ባለሥልጣናት" ይቅርታ እንደማያደርጉ አስታወቁ
(በዘካሪያስ ስንታየሁ/ 02 January 2011; ሪፖርተር ጋዜጣ):- በደርግ ባለሥልጣናት የተገደሉት ስድሳዎቹ የቀዳማዊ ኃይለ ሥላሴ ባለሥልጣናት ቤተሰቦች፣ ለደርግ መንግሥት ባለሥልጣናት ይቅርታ እንደማያደርጉ ባለፈው ሐሙስ ባወጡት መግለጫ ለአቡነ ጳውሎስ አስታወቁ፡፡ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ፓትሪያርክ አቡነ ጳውሎስ የስድሳዎቹን የቀዳማዊ ኃይለ ሥላሴ ባለሥልጣናት ቤተሰቦችን በደርግ ባለሥልጣናት የይቅርታ ጉዳይ ላይ ሊያነጋግሯቸው በቅድስት ሥላሴ ቤተ ክርስቲያን ባለፈው ረቡዕ የቀጠሯቸው ቢሆንም፣ አቡኑ ከቁልቢ ገብርኤል ለቀጠሮው መድረስ ባለመቻላቸው፣ የቀጠሮው ቀን ወደ ሐሙስ ሊተላለፍ ችሏል፡፡
(Read More ወደሚቀጥለው ገጽ ይዞራል . . . . .)