የቅድስት ሥላሴ መንፈሳዊ ኮሌጁ ደቀ መዛሙርት የምግብ ቤቱ ሐላፊ እንዲነሡላቸው ጠየቁ


(ደጀ ሰላም፤ ኖቬምበር 19/2010፤ ኅዳር 10/2003 ዓ.ም)የቅድስት ሥላሴ መንፈሳዊ ኮሌጅ ደቀ መዛሙርት በምግብ አቅርቦት ጥራት፣ በጤና አገልግሎት ሽፋን፣ በሥርዐተ ትምህርት ጫና እና የደቀ መዛሙርት መማክርት መቋቋምን አስመልክቶ ለተቋሙ አስተዳደር ያነሷቸው ጥያቄዎች፣ “ወቅታዊ ምላሽ እና ተገቢ ትኩረት አልተሰጣቸውም” በሚል ከትናንት አንሥቶ በካፊቴሪያው ባለመመገብ እና ትምህርት በማቋረጥ የጀመሩትን ተቃውሞ ቀጥለው ውለዋል፡፡ ደቀ መዛሙርቱ ዛሬ ጠዋት የበላይ ሐላፊ ሊቀ ጳጳስ ብፁዕ አቡነ ጢሞቴዎስ እና ሌሎች የኮሌጁ አስተዳደር ሐላፊዎች በተገኙበት በተነሡት ጥያቄዎች ዙሪያ ውይይት ማድረጋቸው ተዘግቧል፡፡

(Read More ወደሚቀጥለው ገጽ ይዞራል . . . . .)