የፖሊስ ኮሚሽን ህዝብ ግንኙነት ሃላፊ ከሃገር ኮበለሉ

የዘረኛውና አምባገነኑ ወያኔ አገዛዝ የፌደራል ፓሊስ ኮሚሽን የሕዝብ ግንኙነት ሐላፊና የአዲስ አበባ አትሌቲክስ ፌዴሬሽን ፕሬዝዳንት የነበሩት ኮማንደር ደምሳሽ ሃይሉ በወያኔ ዘረኛነት ተማረው ስራቸውንና አገራቸውን ለቀው በስደት እንግሊስ አገር መግባታቸው ታወቀ::

ኮማንደር ደምሳሽ ሃይሉ በግንቦት ሰባት ስም በመፈንቅለ መንግስት ሙከራ ከተከሰሱ የአማራ የጦር መኮንኖች ጋር የቀረበ ግንኙነት አላቸው ተብለው በወያኔ የደህንነት ሠራተኞች በአይነ ቁራኛ የሚጠበቁ እንደነበሩ ቢታወቅም ከጥቂት የአማራ መኮንኖች ውጪ ሌሎች የሥርዓቱ ታማኞች ናቸው እንዲባሉ ብቻ  የጸረ ሽብርተኝነት ዘመቻ ግብረሃይል ቃል አቀባይ ሆነው ስለግንቦት 7 እስረኞች በሬዲዮና ቴለቪዥን መግለጫ እንዲሰጡ ሲደረግ እንደነበር ይታወሳል።

ኮማንደር ደምሳሽ ሃይሉ የወያኔን አገዛዝ ባገለገሉባቸው በርካታ አመታት የትግራይ ጉጂሌ አባላት የሆኑት የፖሊስ እና የጦር መኮንኖች በሚያሳዩት ዘረኛ አሰራር እጅግ ሲማረሩ እንደቆዩ የሚናገሩ የብ አዴን መረጃ ምንጮቻችን፤ የጸረሽብር ዘመቻ ቃል አቀባይ ሆነው ያገለግሉ በነበረበት ወቅት ሳይቀር በሽብርተኝነት ሥም ስለሚታሠሩም ሆነ ኢላማ ሰለሆኑ ሰዎች ከርሳቸው ይልቅ በማዕረግና በደረጃ ከርሳቸው የበታች የሆኑ የትግራይ ተወላጅ የበለጠ መረጃ ያገኙ እንደነበር ይናገራሉ።

የጎጃም ተወላጅ የሆኑት ኮማንደር ደመላሽ ሃይሉ ወያኔን የተቀላቀሉት በጸረ ደርግ ትግል ወቅት እንደሆነ ይታወቃል። በመለስ ዜናዊ የሚመራው ዘረኝ እና ፋሽስት አገዛዝ በተለይም በአማራና የኦሮሞ ተወላጆች ላይ ይህ ቀረሽ የማይባል በደልን ሲፈጽም እንደቆየ መረጃዎችን በማስደገፍ በተከታታይ ስንዘግብ የቆየን መሆናችን አይዘነጋም:: በተለይም በቅርቡ ከወያኔው አምባገነን አገዛዝ ቃሊቲ እስር ቤት ሾልኮ በወጣ መረጃ ዘረኛው አገዛዝ የአማራ እና የኦሮሞ ተወላጆ ላይ የሚፈጽመው ሰቆቃ በቃላት መግለጽ የሚያስቸግር እና ለሂሊና የሚሰቀጥጥ እንደሆነ ስታወቅ የግንቦት 7 እስረኞች በተባሉት አማራ ተወላጆ ላይ በጣም  ጸያፍ የሆነ ስድብ ከመጠቀም ጀምሮ  ብልት ላይ ጠርሙስ ማነልጠልና የዘር ፍሬንም መቀጥቀጥ የመሳሰሉ ዘግናኝ ተግባራትን እየፈጸመ መሆኑ መጋለጡ አይዘነጋም::

ኮማንደር ደምሳሽ በወያኔ ዘረኝነት ከሚማረሩት በርካቶች አንዱ ሲሆኑ ለምን እና እንዴት ከአገር እንደወጡ ወደፊት መረጃ አጠናክረን የምናቀርብ መሆናችንን ከወዲሁ እንገልጻለን።