የወያኔው አምባገነን አገዛዝ ኦብነግ ከፍተኛ ራስ ምታት ሆኖኛል ማለቱ ተጋለጠ

ዊኪሊክስ በቅርቡ ባጋለጠውና በቅርቡ ይፋ በሆነው የአሜሪካ ሚስጥራዊ ሪፖርት በኦጋዴን አካባቢ የሚደረገው የአማጽያን እንቅስቃሴ ከሚጠበቀው በላይ የወያኔውን አምባገነን አገዛዝ እንዳስጨነቀው ታወቀ።  ዘረኛው የወያኔ አምባገነን አገዛዝ ከፍተኛ ጭንቀት ውስጥ መግባቱን  ያጋለጠው ዊኪሊክስ መሰረት ያደረገው በአዲስ አበባ የአሜሪካ አምባሳደር የሆኑት ዶናልድ ያማሞቶ በኖቬምበር 2007 በሚስጢር ያስተላለፉትን ዲፕሎማቲክ መልእክት መሰረት በማድረግ ነው ።  እንደ ዊኪሊክስ መረጃ ዘረኛው አምባገነን አገዛዝ ከፍተኛ ጭንቀት ውስጥ የገባው “ህወሐት ከሁለት አስር አመታት በፊት የደርግን ጨካኝ ስርአትን ሲጥል የነበረበት ይዞታ ከዛሬው የኦብነግ ይዞታ ጋር ተመሳሳይ ሆኖ ስላገኘው ነው በማለት አምባሳደር ያማሞቶ መናገራቸውን ገልጹአል። ” ያማሞቶ “ዘረኛው መለስና አቀንቃኙ የመከላከያ ሚኒስትር ኢታማዠር ሹም ጄኔራል ሳሞራ የኑስ ኦብነግን ሰፊ ድጋፍ ከማግኘቱ በፊት ማስወገዱ ወሳኝ ነው።” ብለው እንደሚያምኑ መጠቆማቸው ታውቁአል።

እንደ ዊኪሊክስ መረጃ አምባሳደሩ ይህንን ግምገማ በግላቸው ያቀረቡት ሳይሆን ከራሱ የኢትዮጵያ መንግስት የመነጨ መሆኑን መጠቆማቸውን፦ የወያኔው ቁንጮ  መለስ፣ ከሳሞራና ከሌሎች የህወሐት/ኢህአዴግ አባላት ጋር ባደረጉት ውይይት “ኦብነግ ወደፊት የመንግስት ስጋት ከመሆኑ በፊት አሁኑኑ በወታደራዊ ክንድ መደቆሱ ወሳኝ ነው ብለው እንደሚያምኑ ግልጽ ሆኗል።” ብሉአል።

ዘረኛውና አምባገነኑ መለስ  በኦብነግ ላይ ያደረትን ፍርሀት የሚገልጸው ግምገማ የተጠቀሰው ኦብነግ በአንድ የቻይና ነዳጅ ፈላጊ ቡድን ላይ ጥቃት ካደረሰና በአጸፋውም የመንግስት ጦር በጭካኔ የተሞላ የመልሶ ማጥቃት እርምጃ ከወሰደ ከጥቂት ወራት በኋላ ሲሆን የመልሶ ማጥቃቱ እርምጃ ከልክ ያለፈና ፍጹም በጭካኔ የተሞላ እንደነበር የስርአቱ ሁነኛ ወዳጅ የሆኑት አሜሪካዊው አምባሳደር ሳይቀሩ ማመናቸው ታውቁአል።

ይሄው የአሜሪካው ሚስጢራዊ መልእክት፤ ጦሩ ከልክ ያለፈ ሀይል መጠቀሙንና ንጹሀን የአካባቢውን ህዝብ በአማጺያኑና በመንግስት ኃይሎች መሀል አጣብቂኝ እንዲገባ እንዳደረገ በተለያዩ የሰበአዊ መብት ተሟጋቾች ቀርቦ የነበረውን ክስ ትክክለኝነት እንደተረጋገጠም ታውቁአል። ይሁን እንጂ ዘረኛው የወያኔ አገዛዝ ይህንን የሰበአዊ መብት ተሟጋች ድርጅቶች ክስ አይኔን ግምባር ያድርገው በማለት በጽኑ ያስተባብለው እንደነበር ይታወሳል።

አምባሳደር ያማሞቶ በቻይና ነዳጅ ፈላጊዎች ላይ በኦብነግ የተወሰደው “በአስደንጋጭ ሁኔታ የተሳካ” ጥቃት ለምን በኢትዮጵያ መሪዎች ላይ ከፍተኛ ፍርሀት እንዳነገሰ ሲገልጹ፦ ‘የመከላከያ ኃይሉ የነዳጅ ፍለጋ ጣቢያውን መከላከልም ሆነ በአጥቂዎቹ ላይ አፋጣኝ እርምጃ መውሰድ ባለመቻሉ እፍረት የተከናነበበት በመሆኑ ነው።” ማለታቸውን ዊኪ ሊክስ አጋልጡአል። ዘረኛው የወያኔ አገዛዝ  ኦብነግ በሽብርተኝነት እንዲመዘገብለት በአሜሪካና በጎረቤት የአፍሪካ ሀገራት ላይ ግፊት ቢያሳድርም እንኳን እስካሁን ከኬንያ በቀር የተቀበለ እንዳልተገኘ  ይታወቃል

አምባገነኑና ዘረኛው የወያኔ አገዛዝ ዓለም አቀፍ የሆኑ የሰብአዊ መብት ጥበቃ ድርጂቶች የሚያቀርቡአቸውን ሪፖርቶች ሁሌም አይኑን በጨው እያጠበና አላየሁም አልሰማሁም እንደሚል የሚታወቅ ሲሆን ኡጋዴን ላይ የወሰደውን በጭካኔ የተሞላበትም ግድያ “የውጭ ሰርጎ ገቦችንና አክራሪዎችን” ለማስቆም ነው ማለቱን ቀደም ብለን መዘገባችን አይዘነጋም።