አየር መንገድ ቦይንግ አውሮፕላኖችን ለመግዛት ከ1.4 ቢሊዮን ዶላር በላይ ብድር እያፈላለገ ነው

የኢትዮጵያ አየር መንገድ 15 የቦይንግ ኩባንያ ስሪት አውሮፕላኖችን ከተለዋጭ ሞተሮቻቸው ጋር ለመግዛት የሚያስችለውን 1.45 ቢሊዮን ዶላር ብድር እያፈላለገ መሆኑ ተገለጸ፡፡ ብድሩን ካገኘ አሥር B787-8 እና አምስት B737-800 ቦይንግ አውሮፕላኖችን ይገዛል፡፡