የደርግ ባለሥልጣናትን ሕዝቡ ይቅርታ እንዲያደርግላቸው የሃይማኖት መሪዎች ሊለምኑ ነው

(በታምሩ ጽጌ)

በሞት እንዲቀጡ ተፈርዶባቸው ቅጣታቸውን በመጠባበቅ ላይ ያሉትን የደርግ መንግሥት ባለሥልጣናትን፤ ጉዳት የደረሰበትም ይሁን ድርጊታቸውን በታሪክ የሚያውቀው የኢትዮጵያ ሕዝብ ይቅርታ እንዲያደርግላቸው፣ አራት የሃይማኖት መሪዎች ታህሣሥ 16 ቀን 2003 ዓ.ም. ሕዝቡን በይፋ ሊለምኑ መሆኑን ምንጮች ለሪፖርተር ገለጹ፡፡