ሰላም ባስ በ20 ሚሊዮን ብር ወጪ ያስመጣቸውን አውቶቡሶች ሥራ ሊያስጀምር ነው

 

– በአንድ ዓመት 257 ሺሕ መንገደኞችን አጓጉዟል

(በዳዊት ታዬ)

ሰላም ባስ አክሲዮን ማኅበር ከ20 ሚሊዮን ብር በላይ በሆነ ወጪ በግዥ ያስመጣቸውን አሥር አውቶቡሶች ወደ መስመር ሊያስገባ መሆኑን አስታወቀ፡፡