ጋዜጠኛ እስክንድር ነጋ በኢትዮጵያ ወቅታዊ ሁኔታ ላይ ማብራሪያ ሊሰጥ ነው
Ethiopia Zare ( ቅዳሜ መጋቢት 3 ቀን 2003 ዓ.ም. March 12, 2011)፦ ሚኒሊክ፣ አስኳልና ሳተናው በተባሉት ጋዜጦቹ የሚታወቀውና በአሁኑ ሰዓት በህትመት ስራ ላይ እንዳይሳተፍ የታገደው ጋዜጠኛ እስክንድር ነጋ፤ በተለይ ለአቶ መለስ ዜናዊ በጻፈው ግልጽ ደብዳቤና በወቅታዊ የኢትዮጵያ ጉዳዮች ዙሪያ በሬዲዮ ውይይት እንደሚያደርግ ተገለጸ።