ሠላማዊ ትግል ሞተ ወይስ የኛ ወኔ ተበጠሰ? (ያሬድ አይቼህ)
ያሬድ አይቼህ
የኢትዮጵያ አገራዊ ፖለቲካ ላይ ገንቢና ጠቃሚ ተጽዕኖ ለማድረግ ከዲያስፖራ የሚደረገው ጥረትና ትግል ከምርጫ 2002 ማግስት ጀምሮ አቅጣጫው ተሰበጣጥሯል። በተለይ ሠላማዊ እና ህጋዊ ትግል ላይ እኔ ተስፋ ስላደረኩ፤ ከኢህአዴግ 99.6% ወንበር ማግበስበስ በኋላ የኢትዮጵያ የዴሞክራሲ ሂደት በጣም ጭጋጋማ፤ ጨለማ፤ ድንግዝግዝና ተስፋ አስቆራጭ ሆኖብኝ ነበር።