የአክብሮትና የሰማዕታት መታሰቢያ ቀናት እንደሚከበሩ ተገለጸ
ማትያስ ከተማ
Ethiopia Zare (ረቡዕ ጥቅምት 24 ቀን 2003 ዓ.ም. November 3, 2010)፦ የፊታችን ቅዳሜ ጥቅምት 27 ቀን 2003 ዓ.ም. (ኖቬምበር 6 ቀን 2010 እ.ኤ.አ.) በስዊድን የሚገኙ ኢትዮጵያውያን የወ/ት ብርቱካን ሚደቅሳን መፈታት አስመልክቶ ”የአክብሮት ቀን” ብለው የሚያከብሩ ሲሆን፣ እሁድ ጥቅምት 28ን (ኖቬምበር 7ን) ደግሞ ምርጫ 97ን ተከትሎ ለተጨፈጨፉት የሰማዕታት ቀን መታሰቢያ ሊያከብሩ ነው። በዝግጅቱ ላይ ዳኛ ወልደሚካኤል መሸሻ ይገኛሉ።