የአቶ መለስ ዜናዊ ደብዳቤ
በሸዋይልማ ኪዳኔ
የኢትዮጵያ ህዝቦች አብዮታዊ ዴሞክራሲያዊ ግንባር (ኢህአዴግ)
Ethiopian Peoples‘ Revolutionary Democratic Front (EPRDF)
ጉዳዩ፦ የወ/ት ብርቱካንን አፈታት አስመልክቶ የተሰጠ ማብራሪያ
የወይዘሪት ብርቱካን ሚደቅሳን ከእስር ቤት በምህረት መለቀቅን አስመልክቶ በቀበሌ፣ በወረዳ እና በዞን ደረጃ በሚገኙ አባላትና ካድሬዎቻችን እንዲሁም በዳያስፖራ በሚገኙ ደጋፊዎቻችን ዘንድ የመንግሥትን እርምጃ በሚገባ አልተረዱም የሚሉ ዘገባዎች በተደጋጋሚ ስለቀረቡልኝ፤ ይህን ደብዳቤ እንደ ጠቅላይ ሚኒስትርነቴ ሳይሆን እንደ ኢህአዴግ ሊቀመንበርነቴ ለመጻፍ ተገድጃለሁ።