ሰቆቃ በወያኔ እስር ቤቶች

ይድረስ ለኢትዮጵያውያን በሙሉ በያላችሁበት

ጉዳዩ፦ በወያኔ እስር ቤቶች ሞልቶ ስለፈሰሰው የወገኖቻችሁ ስቀይና ሰቆቃ እንድታውቁት

ትንሽ ስለራሳችን፡

በወያኔ የወንጀል ምርመራ፣ የወህኒና እስር ቤቶች አስተዳደር አካባቢ የምንሠራ የፖሊስ፣ የፌደራልና የደህንነት ባልደረቦች ነን በአጭሩ እንድታውቁት የምንፈልገው በሀገሪቱ የእስር ቤቶችና ማዕከላዊ እየተባለ በሚጠራው በአዲስ አበባ ከተማ የሚገኘውን እስር ቤት ጨምሮ ስለሚካሄደው የእስረኞችና የአሳሪዎች ግንኙነት፣ ስለእስረኞች አያያዝ፣ በእስረኞች ላይ ስለሚፈጸም ግፍና ሰቆቃ ማወቅ የምንችልበት የተወሰነ ዕድል ያለን ሰዎች መሆናችንን ነው።