በቦስተንና አካባቢው ለምትገኙ ኢትዮጵያውያን በሙሉ!!
ግፍኛውና ጨቋኙ የኢትዮጵያው ጠቅላይ ሚኒስተር መለስ ዜናዊ በኒዮርክየሚገኘው ኮሎምቢያ ዩኒቨርሲቲ ባደረገለት ጥሪ መሰረት እንደሚገኝ ተረጋግጦል። ይህንን ጥሪ በመቃወምና እንዲሁም የዲሞክራሲ አርብኛ የሆነችው ዳኛ ብርቱካን ሚደቅሳና ሌሎችም የፖለቲካ እስረኞች ከስር እንዲለቀቁ ድምጻችንን ለማሰማት እንድንችል የቦስተንና አካባቢው የአንድነት ድጋፍ ድርጅት ዝግጅት አድርጓል።
ወደንዮርክ ለመጓዝ የነጻ ትራንስፖርት የተዘጋጀ ስለሆነ በዚህ ቦታ በመገኘት ተግባራዊ ምላሽ መስጠት የወቅቱ አንገብጋቢ ጥያቄ ስለሆነ
ዓላማውን የምትደግፉ ሁሉ በስልክ ቁጥር 617-785-5495 በመደውል በቅድሚያ መመዝገብ የምትችሉ መሆኑን እንገልጻለን!!
የቦስተንና አካባቢው የአንድነት ድጋፍ ድርጅት ኮሚቴ
ነፃነትና ፍትህ እንዲሁም ዲሞክራሲዊ ስርአት ለኢትዮጵያ!!!