በእርስ በርስ ጦርነት ድል ሃያ አምስት ዓመት ፉከራ

ይገረም አለሙ

Ginbot 20, 25th anv. ግንቦት 20፣ 25ኛ ዓመት

በእርስ በርስ ጦርነት ከሁለቱም ወገን የሚሞተው የአንድ ሀገር ልጅ ነው። አባትና ልጅ፤ ወንድምና ወንድም ከዛና ከዚህ ተሰልፈው የሚገዳደሉበት አጋጣሚም ይኖራል። ይህም በ17 ዓመቱ የርስ በርስ ጦርነት በግልጽ ታይቷል። ወያኔዎች ለድል የበቁት የኢትዮጵያን ሠራዊት ብቻ ሳይሆን ደርግን ተቃውመው ብረት ያነሱ፤ ነገር ግን ከዋሉ ካደሩ ለህወሓት ህልውና አስጊ ይሆናሉ ያሉዋቸውን ድርጅቶች ጭምር (ለምሳሌም ኢህአፓ፣ ኢዲዩ፣ …) ተዋግተው፤ ከዚህም አልፎ በህወሓትም ውስጥ የተለየ አስተሳሰብ ያራመዱ ወይንም ለሥልጣን ያሰጋሉ የተባሉትን እያሰቃዩና እየገደሉ በመሆኑ፤ መገዳደሉ በአንድ ሀገር ልጆች መካከል ከመሆን አልፎ በቤተሰብ መካከል ጭምር እንደነበር አሌ አይባልም። ለዚህ ደግሞ ሩቅ መሄድ ሳያስፈልግ በኢህአፓነቱ በወያኔ እንደተገደለ የሚነገረውን የአቶ በረከት ስምኦን ወንድም መጥቀስ ይቻላል።

ሙሉውን አስነብበኝ …