እነ ‘አሽከር’ ወለተ አማኔል በአደዋ ድል ይታወሱ!
አትክልት አሰፋ (ቫንኩቨር-ካናዳ)
ከ116 ዓመት በፊት በዚህች እለት ድል የሚባል ታላቅ ነገር በዚያች ኢትዮጵያ የምትባል የአለም ግምባር የነበረችና መልሶ ደግሞ ደብዛዋ በጠፋ ሀገር ላይ ተበሰረ። እናም ታላቅ ደስታ ከታላቅ የደም ጎርፍ በሗላ ሆነ። ከድንቅ የጦር ውሎ ለጥቆ፤ ያለ አቻ የተደረገ የግንባር ለግንባር ጦርነት ከተጠናቀቀና የነ አትንኩኝ ባይ ምድር ላይ የደም ጎርፍ ከተጥለቀለቀ በሗላ በኢትዮጵያ ምድር ነጻነት ይፋ ተደረገ። በአለም ዙሪያ ያሉ ጥቁር ህዝቦችም ሰው መሆናቸውን፤ ማሸነፍ ምን ማለት እንደሆነ አውቀው የነጻነትን ተስፋ ይሰንቁ ዘንድ አፍታም አልወሰደባቸውም።