የጅብ እርሻ የዶር. ዳኛቸው መዝገብ

ፕሮፌሰር መስፍን ወ/ማሪያም

የዶ/ር ዳኛቸው የጅብ እርሻ የኢትዮጵያን ሁኔታ በትክክል የሚገልጽ ጽሑፍ ነበር፤ ብዙ ሰዎች እንዳነበቡት ተስፋ አደርጋለሁ፤ ካላነበቡት ፈልገው ቢያነብቡት ማወቅ ለሚፈልጉ ሰዎች ይጠቅማል፤ ዳኛቸው ከመንገድ ላይ ያገኛትን የአነጋገር ፈሊጥ ለቁም-ነገር አበቃት፤ ጅብ በተፈጥሮ ባሕርዩ አያርስም፤ ፍሬም አይለቅምም፤ ድንገት ተሳስቶ ቢያርስም እስቲበቅል ለመጠበቅ ትእግስቱ የለውም፤ ዳኛቸውም የጅቡን እርሻ ‹‹በአንድ በኩል የኢሕአዴግን አካሄድ በሌላ በኩል በተቃዋሚ ፓርቲዎች መሀከል የሚካሄደውን ሁኔታ ሊያስረዳልኝ/ሊገልፅልኝ የሚችል…›› ነው በማለት ይጠቀምበታል።