የመንግስት ሃይሎች የሱሉልታ አንደኛ ደረጃ ተማሪዎች ላይ ጉዳት አደረሱ ። (Photos)

የመንግስት ሃይሎች የሱሉልታ አንደኛ ደረጃ ተማሪዎች ላይ ጉዳት አደረሱ ።
‪#‎Ethiopia‬ ‪#‎OromoProtests‬ ‪#‎Oromo‬ ‪#‎AddisababaMasterplan‬ ‪#‎MinilikSalsawi‬

የመንግስት ሃይሎች በዛሬው እለት የሱሉልታ የአንደኛ ደረጃ ተማሪዎች የመብት ጥያቄ በመጠየቃቸው በጫንጮ ከተማ ተማሪዎች ላይ ጉዳት አደረሱ ።የኦሮሞ ተማሪዎች የአዲስ አበባን ማስተር ፕላን በመቃወም ተቃውሞዋቸውን አጠናክረው የቀጠሉ ሲሆን በዛሬው እለት በምዕራብ ወለጋ ግሊሶ ከተማ ጉታ አበራ የተበላ ተማሪ መገደሉ ታወቀ ።

በተመሳሳይ ሁኔታ በደቡብ ምእራብ ሸዋ በበቾ ከተማ በቱሉቦሎ እንደዚሁም በወሊሶ ክልል በዲላላ ከተማ ውስጥ ከፍተኛ ተቃውሞ ተማሪዎች እያደረጉ እንደሆነ OMN ዘገበ ።በሃረማያ ዩኒቨርስቲይ ውስጥ ተቃውሞ በማድረጋቸው ምክንያት ተደብድበው ከነበሩት ተማሪዎች ማሃል አንድ ተማሪ በዩንቨርስቲው ክሊኒክ በዛሬው እለት ህይወቱ እንዳለፈ ታወቀ።