ባሌ ሮቤን መደወላቡ ዩንቨርስቲ ውጥረት ላይ ናቸው::የመዳወላቡ ዩንቨርስቲን ከከተማዋ የሚያገናኘው መስመር ታጥሯል::
በባሌ ሮቤ የፌዴራል ፖሊስ እና የአግኣዚ ጦር አባላት በከተማው ደርሰው በመፍሰስ እንዲሁም ከገጠሩ ወደ ከተማው የሚያስገቡ መንገዶችን በመዝጋት ከተማዋን ውጥረት ውስጥ ከተዋታል::የሮቤ መምህራን ኮሌጅን የሁለተኛ ደረጃ እና የመጀመሪያ ደረጃ ትምሕርት ቤቶችን ከበዋል::የመዳወላቡ ዩንቨርስቲ ከከተማው የሚያገናኘው መስመር በወታደሮችኡ ተቆርጦ የታጠረ ሲሆን ወደ ሮቤ ከተማ የሚመጡ የገጠር ነዋሪዎች ክመንገድ እንዲመለሱ ተደርጓል::
በመደወላቡ ዩንቨርስቲ ተማሪዎች እና በወያኔ ሃይሎች መካከል ግጭት እንደተፈጠረ እየተነገረ ቢገም መረጃዎች እንዳይወጡ ወታደሮቹ አከባቢው በመክበብ ከፍተኛ ችግር እና ውጥረት እንደፈጠሩ የአከባቢው ነዋሪዎች ይናገራሉ::ከሁለት ቀ በፊት የመዳ ውላቡ ዩንቨርስቲ ተማሪዎች በእራት ከተመገቡ በኋላ ተቃውሞ ያሰሙ የነበረ ቢሆንም በአከባቢው የአገዛዙ የታጠቁ ሃይሎች ስላልነበሩ ተቃውሞው በሰላም ተጀምሮ መጠናአቀቁ ይታወሳል::
