ህገወጡ ሲኖዶስ የቴሌቭዥን አገልግሎቱን የ24 ሰዓት የሳተላይት ሥርጭት ለማስጀመር ከ12 ሚሊዮን ብር በላይ በጀት አጸደቀ
(አዲስ አድማስ፤ ቅጽ ፲፮ ቁጥር ፰፻፳፬፤ ጥቅምት ፳ ቀን ፳፻፰ ዓ.ም.)
ከጥቅምት 12 ጀምሮ የዓመቱን የመጀመሪያ የምልአተ ጉባኤ መደበኛ ስብሰባ በማካሔድ ላይ የሚገኘው ሲኖዶስ፣ የቴሌቪዥን አገልግሎቱን ለማስጀመር የሚያስችል የብር 12 ሚሊዮን 22 ሺሕ ዓመታዊ በጀት ከትላንት በስቲያ ማጽደቁ ታውቋል፡፡ በጠቅላይ ቤተ ክህነት ጽ/ቤት፣ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን የብዙኃን መገናኛ ድርጅት በሚል ተዋቅሮ ሥራ አስኪያጅ በመሠየምና እስከ 22 ሠራተኞችን በመቅጠር የሚጀምረው አገልግሎቱ፤ ዝግጅቱንና ቀረጻውን በሀገር ውስጥ በማከናወን በሳተላይት እንደሚሠራጭ ተገልጧል፡፡
