የሕወሓትን ጓዳ ከነጫጩቶቿ ያንቀጠቀጠው የፕሮፌሰር መስፍን አዳፍኔ ፍርሃትና መክሸፍ (ምንሊክ ሳልሳዊ)
ሰሞናኛ ከሆኑ ጉዳዮች አንዱ አሸብረው የተሸበሩ የዘረኛ ቡድን ካድሬ የሆኑ የሕወሓት ጫጩቶች የማህበራዊ ሚዲያ ጫጫታ ነው::ምሁር በሽታቸው የሆነ ሕወሓቶች ጫጫታቸው ያተኮረው በፕሮፌሰር መስፍን ላይ መሆኑ ምን ያህል በበታችነት ዛሬም እንደሚያላዝኑ ያሳየ ነው::ፕሮፌሰር መስፍን አዳፍኔ የተባለውን የእኩይ ፖለቲከኞችን ሴራ ፍንትው አድርገው ያሳዩበት መጽሃፍ ከወጣ ጀምሮ ተራሮችን አንቀጠቀጥኩ የሚሉት እነአግበስብሴ ከነጫጩቶቻቸው ዘራፋቸውን ከመጀመራቸውም ሌላ መጽሃፉን የመተቸት/የመገምገም አቅሙ ስላሌላቸው የግለሰብን ሰብእና እስከመንካት ዘልቀዋል::ይህ የሚያሳየው የፕሮፌሰሩ አዳፍኔ የሕወሓትን ጓዳ ምን ያህል እንዳንቀጠቀጠ ነው::
ኢትዮጵያዊው ምሁር ፕሮፌሰር መስፍን ሲጽፉን ሲናገሩም የመጀመሪያቸው አይደለም::ሌሎችን ኢትዮጵያውያን ምሁራን እና ፖለቲከኞች በዘረኞች እና በእኩይ ፖለቲከኞች ላይ መጽሃፍትን ጽፈዋል::የአዳፍኔ ግን በተለየ ሁኔታ የሕወሓትን ቤት አናግቶታል::ሕወሓቶች ከጫፍ እስከ ጫፍ ፕሮፌሰሩ ላይ አፋቸውን አሹለው መነሳታቸው ያለቸው የፖለቲካ እምነት በበታችነት እና በዘረኝነት ላይ ስለተመሰረተ ተዳፍኖ ሳይቀር ስለተጋለጠባቸው መቆምያ መቀመጫ ሲያጡ ታዝበናቸዋል::የሕወሓት ፖለቲካ ምን ያህል በጥቂቶች የዘረኛ አስተሳስብ ላይ እንደተመሰረተ እያየን ያለንበት ሁኔታ ላይ ነው ያለነው::ሕወሕቶች ከነጫጩቶቻቸው ምነው እንዲህ ተራወጡ? የሚጽፉት ሰዎች ደሞ አንድ ወጥ የሆኑ ለምን ሆኑ? ብአዴኖች ኦሕዴዶች የት ገቡ ? ማን የበታችነት ስሜት ውስጥ ዘረኝነትን እንደሚዘፍቅ አዳፍኔ በተግባር እያሳየን ነው:: እድሜ እና ጤና ለፕሮፌሰር መስፍን ወልደማርያም::ኣቦ ተባረክ !!! Minilik Salsawi (ምንሊክ ሳልሳዊ)
