በአባቶች ዕርቀ ሰላም ጉዳይ የተነጋገረው የቅዱስ ሲኖዶስ አስቸኳይ ስብሰባ ተጠናቀቀ
- በስደት በሚገኙት አባቶች የተሾሙትን ጳጳሳት ለመቀበል ስምምነት ላይ ተደርሷል
- ቅዱስ ሲኖዶስን በመወከል የሚነጋገሩት የሰላም ልኡካን ተመርጠዋል
(ደጀ ሰላም፤ ዲሴምበር 23/2010፤ ታኅሣሥ 14/2003 ዓ.ም)፦ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ቅዱስ ሲኖዶስ በስደት ከሚገኙት አባቶች ጋራ የተጀመረውን የዕርቀ ሰላም ንግግር እና ድርድር ጉዳይ ለማስቀጠል በቀረበው ምክረ ሐሳብ (መርሐ ድርጊት) ላይ በመነጋገር ውሳኔዎችን አሳለፈ፡፡ ቅዱስ ሲኖዶስ ትናንት በመንበረ ፓትርያርኩ ባካሄደው የአንድ ቀን አስቸኳይ ስብሰባ በጥቅምቱ የቅዱስ ሲኖዶስ ምልአተ ጉባኤ በተመረጡት እና ሰባት ብፁዓን አባቶችን ባቀፈው ኮሚቴ በቀረበለት ምክረ ሐሳብ ላይ ጠንካራ ውይይት በማካሄድ አጽድቆታል፡፡ በኮሚቴው ከቀረቡት የምክረ ሐሳቡ ክፍሎች መካከል በምዕራቡ ዓለም በስደት በሚገኙት አባቶች የተሾሙትን 13 ጳጳሳት ስለመቀበል እና ቅዱስ ሲኖዶስን በመወከል በዕርቀ ሰላሙ ላይ ስለሚነጋገሩት ተደራዳሪ ልኡካን የተነሣው ሐሳብ የጋለ ክርክር እንደተካሄደበት ተዘግቧል፡፡
(Read More ወደሚቀጥለው ገጽ ይዞራል . . . . .)
