በኦሞ ሸለቆ የ200ሺህ ዜጎች ህይወት አጣብቂኝ ውስጥ ገብቷል!
“አንፈናቀልም” ያሉ እየታሰሩ ነው
Ethiopia Zare ( ሐሙስ የካቲት 8 ቀን 2004 ዓ.ም. February 15, 2012)፦ በደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ የታችኛው ኦሞ ሸለቆ በመባል የሚታወቀው አካባቢ መንግስት በህንድ ኩባንያዎች ከፍተኛ ኢንቨስትመንት ለሚታገዘው ኩራዝ የስኳር ልማት ፕሮግራም እንዲውል 300ሺህ ሄክታር የሚጠጋ መሬት በመመደቡ የአካባቢው ነዋሪዎች ህልውና አደጋ ውስጥ ወደወቋል ሲል አልጀዚራ ዘገበ።