ዩኒቨርሲቲው ለመንበረ ፓትርያርኩ ማሳሰቢያ ምላሽ ሰጠ
- ማሳሰቢያው ‹‹የጣልቃ ገብነት እና የዛቻ ቃል ከመሆን አልፎ ዐመፅን የሚያበረታታ እና የሚያባብስ ሆኖ አግኝተነዋል፡፡›› (የአ.አ.ዩ ፕሬዚደንት ጽ/ቤት)
(ደጀ ሰላም፤ ጃኑዋሪ 13/2011፤ ጥር 5/2003 ዓ.ም)፦ የአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ ፕሬዚደንት ጽ/ቤት የኢ/ኦ/ተ/ቤ/ክ መንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ ጽ/ቤት ከልደተ ክርስቶስ የበዓል ዋዜማ አከባበር ጋራ በተያያዘ የዩኒቨርሲቲው ተማሪዎች ለዩኒቨርሲቲው አመራር ያቀረቡትን አቤቱታ የመስማት፣ ክትትል እና ማጣራት የማድረግ ሥልጣንም ሆነ ሐላፊነት እንዳለው ‹‹የሚያውቀው ነገር እንደሌለ››፣ ከዚህም አኳያ ጠቅላይ ጽ/ቤቱ ታኅሣሥ 28 ቀን 2003 ዓ.ም በቁጥር 1780/8513/2003 ‹‹የቤተ ክርስቲያን ልጆች ለመሥሪያ ቤታችን ስላቀረቡት አቤቱታ›› በሚል ለዩኒቨርሲቲው የጻፈው ደብዳቤ ‹‹በተቋሙ አሠራር ውስጥ ጣልቃ የመግባት ሙከራ ሆኖ እንዳገኘው›› በሰጠው ምላሽ አሳወቀ፡፡
(Read More ወደሚቀጥለው ገጽ ይዞራል . . . . .)