የናይጄሪያ ጦርና የቦኮሃራም ስጋት

በሰሜናዊ ናይጄሪያ የሚንቀሳቀሰው እስላማዊ ቡድን ቦኮ ሃራም የማይዱግሪ ከተማን ለመቆጣጠር ለሁለተኛ ጊዜ የከፈተው ጥቃት አልተሳካም። በዚህ ወር በሚካሄደው የናይጄሪያ ምርጫ ላይ ጥቃት ሊሰነዝር ይችላል የሚል ስጋት በማየሉ የቀጠናው ሃገራት ወታደራዊ እርምጃ ጀምረዋል።