የሊቀ ማእምራን ፋንታሁን ሙጬ ሹመት እያነጋገረ ነው


ሊ/ማእምራን ፋንታሁን ሙጬ
  • ‹‹በቅዱስ ሲኖዶስ ጥፋተኛ የተባለን ሰው ሹመት መስጠት ብቻ  ሳይሆን በሥራ መመደብ ስሕተት ነው፡፡››   (የቅዱስ ሲኖዶስ ዋና ጸሐፊ ተቃውሞ) 
  • በአስተዳደር እና አቅም ግንባታ መምሪያ ቦታ አዲስ ሹመት ተሰጥቷል
(ደጀ ሰላም፤ ኖቬምበር 11/2010፤ ኀዳር 2/2003 ዓ.ም) የአዲስ አበባ ሀገረ ስብከትን በተመለከተ በቅዱስ ሲኖዶስ የተሠየመው አጣሪ ኮሚቴ ለጥቅምቱ የቅዱስ ሲኖዶስ ምልአተ ጉባኤ ባቀረበው ሪፖርት እንዲሁም በ29ው አጠቃላይ የሰበካ መንፈሳዊ ጉባኤ ስብሰባ ላይ በጠቅላይ ቤተ ክህነቱ ዋና ሥራ አስኪያጅ ሪፖርት ውስጥ ተካትቶ በቀረበው የቁጥጥር አገልግሎት ሪፖርት ቃለ ዓዋዲውን ተከትሎ ከመሥራት እና መልካም አስተዳደርን ከማስፈን አኳያ በተገኘባቸው ከፍተኛ ግድፈት የተነሣ ከሥራ አስኪያጅነት ሐላፊነታቸው እንዲወገዱ፣ የፈጸሟቸው በደሎች ሁሉ ተጣርቶ በሕግ እንዲጠየቁ የተወሰነባቸው ሊቀ ማእምራን ፋንታሁን ሙጬ በመንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ ቤተ ክህነት በምክትል ዋና ሥራ አስኪያጅ ማዕርግ የልማት ጉዳዮች ዘርፍ ሥራ አስኪያጅ ሆነው መሾማቸው ጥያቄዎችን እያስነሣ ይገኛል፤ በቤተ ክርስቲያኒቱ ወቅታዊ ችግሮች ዙሪያ በምእመኑ ዘንድ አንድ አቋም እና ግንዛቤ እየተፈጠረ የመጣበትን አትኩሮት ለማስቀየስ የሚደረግ ጥረት አካል ተደርጎም ተወስዷል፡፡

(Read More ወደሚቀጥለው ገጽ ይዞራል . . . . .)