የሰሜን ሸዋ ሀገረ ስብከት ቤተ ክህነቱ ላለበት የአሠራር ብልሹነት ማሳያ ሆነ


  • የሰሜን ሸዋ ዞን አስተዳደር የሀገረ ስብከቱን ሊቀ ጳጳስ አስጠነቀቀ
(ደጀ ሰላም፤ ኖቬምበር 16/2010፤ ኅዳር 7/2003 ዓ.ም) የሰሜን ሸዋ ዞን አስተዳደር ጽ/ቤት የሰሜን ሸዋ ሀገረ ስብከት ለቤተ ክርስቲያኒቱ ልማት መሰናከል እና ለገጽታዋ መበላሸት ዕንቅፋት ሆኖ የሚገኘውን የቤተ ዘመድ አስተዳደር፣ ሙስና እና የሥነ ምግባር ብልሽት በአስቸኳይ እንዲያስተካክል አስጠነቀቀ፡፡ ‹‹ኅብረተሰቡ በሀገረ ስብከቱ ላይ የተቃውሞ ሰላማዊ ሰልፍ ለማድረግ ምክር ቤቱን እስከ መጠየቅ ደርሷል›› ያለው ጽ/ቤቱ “ኃላፊነቱ የተወሰነ የግል ኩባንያ” እስከ መባል የደረሰው የሰሜን ሸዋ ሀገረ ስብከት አስተዳደር በአፋጣኝ ይሻሻል ዘንድ የሀገረ ስብከቱ ሠራተኞች የሚፈጥሩት ጫና እና የኅብረተሰቡ ቁጣ እየተጠናከረ መምጣቱን ለሊቀ ጳጳሱ አስረድቷቸዋል፡፡ ችግሮቹ በምክክር የማይፈቱ ከሆነ ለሕዝቡ ምሬት ምላሽ ለመስጠት ጉዳዩ በሕግ አግባብ የሚታይ ይሆናል ብሏል አስተዳደሩ፡፡

(Read More ወደሚቀጥለው ገጽ ይዞራል . . . . .)