የናይጀሪያ ምርጫ እና የአውሮጳ ህብረት ታዛቢ ቡድን

በናይጀሪያ አጠቃላይ ምርጫ ሊጀመር ሶስት ሳምንታት ገደማ በቀሩት ባሁኑ ጊዜ የአውሮጳ ህብረት የምርጫ ታዛቢ ቡድን አባላት ወደ ናይጀሪያ እንደሚልክ አስታውቋል፣ ይሁንና፣ ታዛቢዎቹ የፀጥታ ችግር ወደሚታይበት ሰሜናዊ የሀገሪቱ ከፊል እንደማይሠማሩ የታዛቢው ቡድን መሪ ሳንቲያጎ ፊሳስ ገልጸዋል።