ኪንሻ-የተቃዉሞ ሠልፍ፤ ግጭትና ግድያ

የኮንጎ ዴሚሞክራቲክ ሪፐብሊክ ፕሬዝዳንት ጆሴፍ ካቢላ ዘመነ-ሥልጣናቸዉን ለማራዘም ማቀዳቸዉን በሚቃወሙ ሠልፈኞችና በፀጥታ አስከባሪዎች መካከል ትናንት የተጀመረዉ ግጭት ዛሬም እንደቀጠለ ነዉ።