ከጓድ መንግስቱ ኃይለማርያም ‹‹ትግላችን›› ጋር…
ተመስገን ደሳለኝ
ማን ይፈራል ሞት
ማን ይፈራል
ለእናት ሀገር ሲባል..
የጊዜው ወታደራዊ ደርግ አስተዳደር፣ የአብዮታዊ ጦር ሰራዊት ጠቅላይ አዛዥ፣ የኢትዮጵያ ሰራተኞች ፓርቲ ዋና ፀሀፊ፣ የኢህዴሪ ሊቀመንበር፣ የኢትዮጵያ ፕሬዘዳንት… ጓድ መንግስቱ ኃ/ማርያም ሰሞኑን በስደት ከሚኖሩበት ዙምባቤ ‹‹ትግላችን›› የተሰኘ መጽሐፍ አሳትመው በ39 የአሜሪካ ዶላር እየቸበቸቡ ነው። በእርግጥ ሀገር ከመሸጥ መጽሐፍ መሸጥ የተሻለ ነበር።