ሹምሽር በጋምቤላ

የጋምቤላ ህዝቦች ዴሞክራሲያዊ ንቅናቄ (ጋህዴን) የዉስጥ ግምገማ አካሂዶ የድርጅቱን የአመራር አባላት መለወጡን የፓርቲዉ አዲስ ሊቀመንበር ለዶይቼ ቬለ ገለጹ።

አቶ ገልዋክ ቱት የጋህዴን የቀድሞ ሊቀመንበር ከሙስናና መሰል የአስተዳደር ግድፈቶች ጋ በተገናኘ ስልጣናቸዉን እንዲለቁ መደረጉን የሚገልፁ ዘገባዎች የተዛቡ ናቸዉ ብለዋል። የአዲሲቱ ኢትዮጵያ የጋራ ንቅናቄ የተሰኘዉ ተቋም ሊቀመንበር ደግሞ በግምገማ ወቅት የአኙዋክ ጎሳ አባላትን ግድያ በሚመለከት ተናገሩ የተባለዉ የሰብዓዊ መብት ጥሰት ላይ ለሚያቀርቡት ክስ ጠቃሚ መረጃ ነዉ ይላሉ። ያዳምጡ