ባህላዊዉ የገና በዓል አከባበር

በኢትዮጵያዉያን ዘንድ የበዓላት ሁሉ በኩር የሆነዉ የልደት ማለት ገና በዓል ትናንት በደማቅ ተከብሮ ዉሎአል። በኢትዮጵያ የክርስትና ሐይማኖት ተከታዮች አርባ ቀን ፆመዉ የምሥራች የዓለም ቤዛ ክርስቶስ ተወለደ ሲሉ የልደትን በዓል በምሥራች በደስታ ያከብሩታል ተድላዉ ደስታዉም የተጋነነ ነዉ ሲሉ የሃይማኖት አባቶች ይናገራሉ።