በኦነግ አዲስ አቋም ዙሪያ ውዝግቡ ቀጥሏል
“በኦነግ ውስጥ የተፈጠረው ችግር ምክንያት የጠራ ራእይ ማጣት ነበር” የኦነግ ከፍተኛ አመራር
Ethiopia Zare (ሐሙስ ታህሳስ 26 ቀን 2004 ዓ.ም. January 5, 2011)፦ በፈረንጆችቹ አዲስ አመት መግቢያ የኦሮሞ ተወላጆች በብዛት ይኖሩባታል በምትባለው ሜኔሶታ ክፍለ ከተማ በተጠራ ህዝባዊ ስብሰባ ላይ ይፋ የሆነውና ኦነግ (የኦሮሞ ነጻነት ግንባር) ከተመሰረተበት ከ1960 እኤአ ጀምሮ ለመጀመሪያ ጊዜ የኢትዮጵያን አንድነት የተቀበለበትን መግለጫ ካወጣ ጀምሮ የተለያዩ አስተያየቶች በመሰማት ላይ ናቸው።