ያልተዘመረላቸው ጀግኖች
የኔሰው ጓንጉል [email protected]
”ሀሳብን በነጻ የመግለጽ መብት ከሰጪው የተለየ ሀሳብ ላለው ካልተሰጠ መብቱ እርባና ቢስ ነው።”
ሮዛ ሉክዘምበርግ ለሌኒን ከጻፈችው ደብዳቤ
ከሁለት ዓመት በፊት ኢትዮጵያ እያለሁ ከጠዋቶች ሁሉ የሚናፍቀኝ የቅዳሜው ነበር። የእረፍት ቀን ስለሆነ ወይም አርፍዶ ለመነሳት አልነበረም። ቅዳሜ ጠዋት መኪናዬ ውስጥ ቁጭ ብዬ የ”ካልዲ”ን ማኪያቶ እየተጎነጨሁ፤ ለስላሳዋ ጸሀይ እየዳበሰችኝ፤ ደስ የሚል ሙቀት እየፈጠረችብኝ ”አዲስ ነገር”ን ጋዜጣ ለማንበብ ነበር።