ዩክሬን ከማይዳን አብዮት እስከ ባይደን ጉብኝት

ከቀዝቃዛዉ ጦርነት ፍፃሜ ወዲሕ በተለያዩ ሐገራት የተለያዩ የአደባባይ ሠልፍ-አመፆች ተደርገዋል።አስር ዓመት ባልሞላ ጊዜ ሁለት መንግሥት በአደባባይ አመፅ የፈረሰባት ሐገር ግን አንድ ናት።ዩክሬን።ዛሬም ቢያንስ ምሥራቃዊ ግዛቷ ደም በሚያራጭ አመፅ እየወደመች፤ ምስራቅ ምዕራቦችን ከ25 ዓመት በኋላ ዳግም እንዳፋጠጠች ነዉ።