የኢሕአዴግ መንግስት ለአምባሳደሩ መታሰር በቂ መልስ አላቀረበም
“የዓለም አቀፍ ህግጋትን ጥሰዋል” የስሎቫክ የውጭ ጉዳይ ሚኒስተር
Ethiopia Zare ( ቅዳሜ ኅዳር 9 ቀን 2004 ዓ.ም. November 19, 2011)፦ አጠያቂ በሆነ መልኩ በኢህአዴግ ታጣቂ የጸጥታ ኃይሎች ተይዘው ለ3 ቀናት በእስር የቆዩትን አምባሳደር በተመለከተ የኢትዮጵያ መንግስት እጅግ ዘግይቶ የሰጠው ምላሽ አጥጋቢ አይደለም ሲሉ የስሎቫክ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር አወገዙ።