የአምባሳደር መናፈሻ ሠራተኞች ከሥራችን ልንፈናቀል ነው አሉ

በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የውበት፣ የመናፈሻ፣ የዘላቂ ማረፊያ ልማትና አስተዳደር ኤጀንሲ፣ ከሚያስተዳድራቸው መናፈሻዎች አንዱ የሆነው አምባሳደር መናፈሻ ሠራተኞች፣ ከሥራቸው ሊፈናቀሉ መሆኑን በመግለጽ መንግሥት እንዲታደጋቸው ጠየቁ፡፡