ወጣት ሙስሊም አክራሪዎች በጀርመን

«ለቅዱስ ጦርነት» እየተባለ በምዕራብ ሀገራት የሚገኙ ወጣት ሙስሊሞች እየተሰበኩ መሰደዳቸውን ቀጥለዋል። ለዚህም ለቅዱስ ጦርነት የሚሰብኩ እና የሚመለምሉ ጀርመን ሀገርም አልጠፉም። በሶርያ ብቻ ከ 74 ሀገራት የተመለመሉ 12 000 የሚደርሱ የውጭ ሀገር ዜጎች እንዳሉ ይገመታል።