የቦኮ ሃራም ግሥጋሴ

ናይጀሪያ ዉስጥ የሚንቀሳቀሰዉ እስላማዊ ፅንፈኛ ታጣቂ ቡድን የሚፈጽማቸዉን የኃይል ርምጃዎች እያጠናከረ በመሄድ ላይ ነዉ። በሰሜን የሀገሪቱ ክፍል በያዝነዉ ሳምንት መጀመሪያ አንዳንድ ከተሞችን መቆጣጠሩ የሚነገርለት ይኸዉ ቡድን ቀጥሎ የቦርኖ ግዛት ዋና ከተማ ማይዱጉሪን ሊይዝ ይችላል የሚል ስጋትም ይሰማል።