የኃየሎም አርአያ አሟሟት (የመጨረሻ ክፍል)

በዳዊት ከበደ ወየሳ (አትላንታ)

ይህ የመጨረሻው ክፍል ነው። የመጨረሻውን ክፍል ከማቅረቤ በፊት የጽሁፌን አሃድ በምስጋና ልጀምር። ሁልጊዜ በህሊናዬ የነበረውን… ነገር ግን ለመጻፍ ጊዜ አጥቼ በነበረበት ወቅት ብርታት ለሆነኝ የእውነት እና የፍቅር አምላክ ምስጋና ይጋባው። ምንም እንኳን ባላነበውም ስለጽሁፉ በሰማሁ ጊዜ… ይህንን ታሪክ ለመጻፍ ምክንያት የሆነኝን የኢትዮ ሚዲያ ባለቤት አብርሃ በላይን በንፁህ ልቤ አመሰግነዋለሁ። ይህንን ጽሁፍ በነጻ ህሊና በድረ ገጾቻችሁና በሬዲዮናቸው ላይ ላቀረቡ ጋዜጠኞች፤ እንዲሁም ጊዜያቸውን ወስደው ይህን ታሪክ በመስማትና በማንበብ (ብትቀበሉትም ባትቀበሉትም) በጨዋ ኢትዮጵያዊነት ሃሳብ የሰጡኝን በሙሉ… በጽሁፍ ምስክርነታችውን የሰጡኝንም ጭምር፤ እኔም በተራዬ እጅ በመንሳት “እግዚአብሄር ያክብርልኝ” እላለሁ።