አንተም እንደ የሱስ የኔሰው ገብሬ
አንተ ያገሬ ልጅ
እስኪ ልጠይቅህ
የነጻነት ትርጉም
እንደምን አስተዋልህ
በመለሰ ዘመን
ለጥብሥ ያበቃህ
እኔ በሚገባኝ
የሱስ ብቻ ነበር
ባልሰራበት ሐጢት
ራሱን የሰዋ
ያውም ለዓመጹበት
እጅጉን ይገርማል
አንተም መሰዋትህ
በኢትዮጵያዊነት
ሞትማ ይመጣል
ሁሉን አስተካካይ
አንተ ያገሬ ልጅ
እስኪ ልጠይቅህ
የነጻነት ትርጉም
እንደምን አስተዋልህ
በመለሰ ዘመን
ለጥብሥ ያበቃህ
ዋጋ ከፍሎዋል አሉ
ብዙ ኢትዮጵያዊ
ለፍትህ ለነጻነት
ያንተ ረቀቀ እንጅ
ለነጻነት ስትል
እንደ ወርቅ ማዕድን
በእሳት ውስጥ መንጠርህ::
©ለምለም ጸጋው፣ ለ የኔሰው ገብሬ መታሰቢያ የተጻፈ፣ህዲር 7 ቀን 2004 ዓ/ምህር
“ፍትህና ዱሞክራሲ ሌለበት አገር አልኖርም በሚል ምክንያት ራሱን በእሳት አቃጥሎ የገደለው መምህር የኔሰው
ገብሬ የቀብር ስነስርአት ተፈጸመ፣ ህዲር 5 ቀን 2004 ዓ/ም” (http://www.ethiopatriots.com/images/be%20esat%20meqatel%20111115.pdf)