የሶሪያ አማፅያን የኔቶ ጣልቃ ገብነት አያስፈልገንም አሉ

ለስምንት ወራት የዘለቀውን የሶሪያ ሕዝባዊ አመፅ የመሩት ተቃዋሚዎች የሶሪያን መንግሥት ለማስወገድ የሰሜን አትላንቲክ የጦር ቃል ኪዳን ድርጅት (ኔቶ) ድጋፍና ጣልቃ ገብነት እንደማያስፈልጋቸው አስታወቁ፡፡