የየመን የረሐብ ሥጋት

ከግማሽ የሚበልጠዉ የየመን ሕዝብ ሠብአዊ ርዳታ እንደሚያሥፈልገዉ የተባበሩት መንግሥታት የሠብአዊ ርዳታ ማስተባባሪያ ቢሮ (OCHA በምሕፃሩ) እስታወቀ።OCHA እንደሚለዉ ለችግር ለተጋለጠዉ የመናዊ እስቸኳይ ርዳታ ካልደረሰ ለመገመት የሚከብድ ሠብአዊ ድቀት መከሰቱ አይቀርም።