ወ/ት ብርቱካን ሚደቅሳ እንድትፈታ ለተሟገቱ ካናዳዊያን የምስጋና ዝግጅት ተሰናዳ
በተለይ ክቡር ሚስተር ፒተር ጁሊያንና ፓርቲያቸው አብዩን ሚና ተጫውተዋል
Ethiopia Zare (ቅዳሜ ጥቅምት 6 ቀን 2003 ዓ.ም. October 16, 2010)፦ ብርቱካን ሚደቅሳ ከእስር እንድትፈታ የካናዳን ፓርላማ በመወትወት የሚታወቁትና የበርናቢ ኒውዌስት ሚኒስትር የኤን. ዲ. ፒ. ፓርቲ የፓርላማ ተመራጭ የሆኑት ክቡር ሚስተር ፒተር ጁሊያንንና አጋሮቻቸውን የሚያከብርና ለብርቱካን መፈታት ያደረጉትን አስተዋጽኦ የሚያደንቅ የምስጋና ስነስርአት በቫንኩቨር ነዋሪዎች መዘጋጀቱ ተገለጸ።