የአፍሪቃውያን ስደተኞች ሁኔታ

ትናንት ታስቦ የዋለውን የዓለም ስደተኞች ቀን ምክንያት በማድረግ የተመድ የስደተኞች ጉዳይ ተመልካች መስሪያ ቤት፣ በምሕፃሩ « ዩ ኤን ኤች ሲአር» ባወጣው ዘገባ ከሁለተኛ ዓለም ጦርነት ወዲህ ትውልድ ሀገሩን ለቆ መሰደድ የተገደደው ሰው ቁጥር እንዲህ እንዳሁኑ በዝቶ እንደማያውቅ አመልክቶዋል።