የኢራቅ ምሥቅልቅል

የአንጎሎ-አሜሪካን መሪዎች አዲሲቱ ኢራቅ በደም-አስከሬን፤ በሽብር፤ እልቂት፤ በጥፋት ዉድመት ቀለል ካለም እስረኞችን በማሰቃየት- ከድፍን ዓለም አንደኛ ሐብታም ሐገር ስትሆን-ሰዉዬዉም እንደ ሁሉም ዓለም አዩ።እንደ ሁሉም ኢራቃዊ ኖሩበት።አማረሩ።እንደ ሐይማኖት መሪ-አወገዙ፤ እንደ ወጣት ጥፋቱን-ሊያጠፋ ተነሳ።