ምክር ያልሰማ ንጉስ ፤ አሟሟቱን ሲያረክስ

ሉሉ ከበደ

ኖቬምበር 5 / 2006 ሳዳም ሁሴን በሞት እንዲቀጣ ሲፈረድበትና ዲሴምበር 30 / 2006 ሲሰቀል  ለስቅላቱ ፍርድ ዋና ወንጀል ሆኖ የቀረበው የክስ ጭብጥ፡ የሚቃወሙት የሺአት ሙስሊሞች በ1982 የመግደል ሙከራ ካደረጉበት በሗላ 148 ቱን ገድሏል ነው። ሚሊዮንም ሰው ይግደሉ፤ አምስት ሰው ይግደሉ፤ የሞት ፍርድ ለመቀበል ሁለትም አስርም በቂ ነው። እንደ አገዳደሉ አይነት። ምርጫ 97 ላይ የኛ ጌታ ንጉስ መለስ ጀግናው ከሁለት መቶ በላይ ግዳይ ጥሏል። ስምንት መቶውን አቁስሏል። ማንም ምንም ያደረገው ነገር አልነበረም በሰላም ለተቃውሞ ሰልፍ ወጣ እንጂ። የሰረቃችሁት ድምጼን መልሱ ብሎ። ይህ ገዳይ ነፍሱ በእስር ላይ መሆንዋን ህሊናው ያለ እረፍት ይነግረዋል:: ይጮህበታል። የፍርዱ ቀን ገና አልታወቀም።