የኖርማንዲ ዘመቻ እና የኃያላኑ አቋም

ጦር አዛዦች ወደ ፊልድ ማርሻል በርናርድ ሞንትጎመሪ እና ወደ ጄኔራል ኦመር ብራንድልያ ዞር አሉና «እንቀጥላለን» አሉ።ሰኔ ስድስት 1944—የኖርማንዲ ሰማይ ሰዉ እንደ ዶፍ-ይዘንብበት ገባ።ሐምሳ ሺሕ የሚገመተዉ የጀርመን ወታደር በመቶ-ሐምሳ ሺሕ የተባባሪዎቹ ሐገራት ወታደሮች ተጥለቀለቀ።ባሕሩም ምድሩም፤ ሰማዩም አስከሬን ይለብቀዉ ያዘ።