ዩክሬይን፤ ፕሮሼንኮ ቃለ ማሃላ ፈፀሙ

አዲስ ተመራጩ የዩክሬይን ፕሬዚዳንት ፔትሮ ፕሮሼንኮ፤ ቃለ ማሃላ ፈፀሙ። በበዓለ ሲመቱ ላይ ከ50 በላይ የዉጭ ሀገር ልዑካን የተገኙ ሲሆን ከመካከላቸዉ የጀርመኑ ፕሬዚዳንት ዮአሂም ጋዉክ፤ የአዉሮጳ ኅብረት ምክር ቤት ፕሬዚዳንት ሄርማን ቫን ራንፖይ እንዲሁም የዩናይትድ ስቴትስ ምክትል ፕሬዚዳንት ጆ ባይደን ይገኙበታል።